8 - ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ የተባረክሽ ነሽ ይሉኛል
- Category: ከእመቤታችን ማርያም ጋር መጸለይ
- Published: Tuesday, 31 August 2010 19:09
- Written by Super User
- Hits: 6234
- 31 Aug
8
‹‹ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ የተባረክሽ ነሽ ይሉኛል››
የእግዚአብሔር ቃል፤- የቅድስት ድንግል ማርያም የምስጋና ጸሎት፤ ሉቃስ 1፡ 46-55
የምስጋና ጸሎት፣ በአዲስ ኪዳን ስለ እናታችን ማርያም እንደሌላው ታሪክ ሁሉ፣ የመጀመሪያ ክርስቲያኖች በማርያም ላይ ያላቸውን እምነት ይመሰክራል፡፡ ማርያም በሐዋርያት ጊዜ ማን ነበረች? እነርሱ፣ ማርያምን እንዴት ይጠሩ፣ ያስታውሱና ያመሰግኑ ነበር? የዚህን ጥያቄን መልስ አዲስ ኪዳንን በማንበብ እናገኛለን ምክንያቱም ወንጌላውያንና ሌሎች ያመኑትንና ለእምነታችን ይጠቅማል ብሎ ያሰቡትን ብቻ ጽፈዋል፤
‹‹ ›› (ዩሐ 20፡ 31)
ማዕከሉ ሁል ጊዜ ክርስቶስ ነው፡፡ በድህንነት ታሪክ፣ በኢየሱስ ተልእኮና በቤተ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ የማርያም ሚና ማወቅ፣ ስለ ኢየሱስና ስለ ወንጌሉ የበለጠ እንድንረዳ ይረዳናል፡፡
በአዲስ ኪዳን እናታችን ማርያም፤
- ድንግል ናት (ሉቃ 1፡ 27፤ ንጽ. ኢሳ 7፡ 14)
- የተወደደች፣ የተባረከች፣ የተመረጠች፣ ጸጋን የተሞላች፣ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ ያገኘች ናት (ሉቃ 1፡ 28-30)፡፡ እነዚህ ስያሜዎች ለማርያም እንደ ስም ነው የሚጠቅሙ፡፡ ስለዚህም አስፈላጊውን ነሕልውናዋን ባህሪ ይገልጻሉ፡፡ ሕይወቷን ሙሉ በእግዚአብሔር የተወደደችና በጸጋው የተሞላች ናት፡፡
- የእግዚአብሔር እናት ናት፤
‹‹ ›› (ሉቃ 1፡ 31-32)፡፡
‹‹ ›› (ሉቃ 1፡ 43)፡፡
- በመንፈስ ቅዱስ የተሞላች ናት፤
‹‹ ›› (ሉቃ 1፡ 35)፡፡ እናታችን ማንፈስ ቅዱስ ከኤልሣቤጥ ጋር ተካፈለች፤
‹‹ ›› (ሉቃ 1፡ 41)፡፡ መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ በወረደ ጊዜ እናታችን ማርያም ከሐዋርያትና ከመጀመሪያ አማኞች ጋር ትጸልይ ነበር (ንጽ. ሐ.ሥራ 1፡ 14፤ 2፡ 1-5)፡፡
- የእግዚአብሔር አገልጋይ ፈቃዱን ለመፈጸምና በእግዚአብሔር የድህንነት ዕቅድ ለመተባበር ዝግጁ ናት፤
‹‹ ›› (ሉቃ 1፡ 38)፡፡ እመቤታችን የመጀመርያና ምሳሌ የምትሆን የክርስቶስ ተከታይ ናት ምክንያቱም እርሷ የእግዚአብሔርን ቃል ተቀበለች፤ አዳምጣም በሥራ ላይ አዋለች፡፡ እርሷ ክርስቶስን ለመከተል ለሚፈልጉ ሁሉ አርአያ ናት፡፡
- በጣም የተባረከች ናት፤
ማርያም የብጽእናን ሕይወት ስለኖረች (በመንፈስ ራሳቸውን ዝቅ የሚያደርጉ፣ የዋሆች፣ ምህረትን የሚያደርጉ፣ ንጹሕ ልብ ያላቸው፣ እርቅና ሰላምን የሚያደርጉ፣ ስለጽድቅ ስደትና መከራን የሚቀበሉ … (ንጽ. ማትዎስ 5፡ 1-12) እርሷ የእምነትና የክርስቶስ ፍጹም ተከታይ ምሳሌ ናት፡፡
እመቤታችንን እያከበርንና እግዚአብሔርን በእናቱ ባደረገው አስደናቂ ነገሮች እያመሰገንን፣ በሕይወታችንና በቤተሰባችን እግዚአብሔር ላደረገው አስደናቂ ነገር በጥልቀት ማሰብ እንችላለን፡፡ በቤተሰባችን የእግዚብሔርን ሕልውና እንገነዘባለን?
በእስራኤላዊያንና በማርያም ታሪክ ውስጥ የሰራው አመላክ አሁንም በእኛ ሕይወት ውስጥ ለመስራት ይፈልጋል፡፡
እስራኤላዊያንና ማርያም እግዚአብሔርን በሕይወታቸው መኖሩን ስለተረዱ፣ ታሪካቸውን ወደ ደኅንነት ታሪክ ለውጠዋል፡፡
እኛም የእግዚአብሔር ሥራ በሕይወታችንና በቤተሰባችን ውስጥ ማየት ከቻልን፣ ታሪካችንን ወደ ደኅንነት ታሪክ መለወጥ እንችላለን፡፡
እንጸልይ፡-
የፍቅርና የምህረት አምላክ ሆይ፣ በመልአኩ መልእክት ቅድስት ድንግል ማርያም ልጅህን ተቀበለችና በመንፈስ ቅዱስህ ብርሃን ተሞላች፣ የቃልህ ቤተ መቅደስ ሆነች ሁል ጊዜ ፈቃድህን ለመፈጸም ዝግጁ የሆነችውን የቅድስት ድንግል ማርያምን ምሳሌነት ለመከተል እርዳን፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እንለምንሃለን፡፡ አሜን፡፡