9- እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፤ የአዲስ ኪዳን ታቦትና እውነተኛ አማኝ ናት
- Category: ከእመቤታችን ማርያም ጋር መጸለይ
- Published: Tuesday, 31 August 2010 19:11
- Written by Super User
- Hits: 9232
- 31 Aug
9
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፤ የአዲስ ኪዳን ታቦትና እውነተኛ አማኝ ናት፡፡
የቃል ኪዳን ታቦት
እግዚአብሔር በሲና ተራራ በድንጋይ ጽላቶች የተጻፈውን ትእዛዛት ለሙሴ የሰጠውንና ሕዝቡ በበረሃ እየተጓዙ እያሉ የሰጣቸውን መና የያዘ ነው፡፡ ታቦቱ እግዚአብሔር በሕዝቡ መካከል ስላለው ንቁና ተወዳጅ ሕልውና ምልክት ነበር፤
‹‹ ›› (ዘሌ 26፡ 11)
ደመና በኢየሩሳሌም ቤተ መቅደሱን እንደሸፈነ
የመንፈስ ቅዱስ ጥላ እናታችን ቅ. ድንግል ማርያምን ሽፈነ፡፡
1 መጸሐፈ ነገሥት 8፡ 10-12 |
ሉቃስ 1፡ 35 |
‹‹ካህናቱ ከቤተ መቅደሱ እንደወጡ ቤተ መቅደሱ ድንገት በደመና ተሞላ፤ በደመናውም ውስጥ የእግዚአብሔር የክብር መገለጥ ብርሃን ያንጸባርቅ ስለነበር ካህናቱ ተመልሰው ለመግባትና አገልግሎታቸውን ለማከናወን አልቻሉም፡፡ በዚህ ጊዜ ሰሎሞን እንዲህ ሲል ጸለየ፤ እግዚአብሔር አምላክ ሆይ አንተ በደማናና በጨለማ ውስጥ መሰወርን ወድደሃል፡፡›› |
መልአኩም እንዲህ ሲል መለሰ፤ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፤ የልዑል እግዚአብሔርም ኀይል በአንቺ ላይ ይሆናል፤ ስለዚህ ከአንቺ የሚወለደው ሕፃን ቅዱስ ነው፤ የእግዚአብሔርም ልጅ ይባላል፡፡›› |
ወንጌላዊው ሉቃስ ማርያም ኤልሳቤጥን ለመጎብኘት ያደረገችውን ጉዞ (ሉቃ 1፡ 39-45) የቃል ኪዳኑ ታቦት ከይሁዳ ወደ ኢየሩሳሌም የመወሰዱ ጉዞ (ንጽ. 2 መጺሐፈ ሳሙኤል 6፡ 1-23) ጋር ያነፃጽራል፡፡ በዚህ ምክንያት እኛ ቅድስት ድንግል ማርያምን ‹‹የአዲስ ኪዳን ታቦት›› ብለን እንጠራታለን፡፡
2 መጸሐፈ ሳሙኤል 6፡ 1-23 |
ሉቃስ 1፡ 39-45 |
በብሉይ ኪዳን ታቦት ውስጥ እገዚአብሔር ለሙሴ ተሰጠው የእግዚአብሔር ቃል ነበር፡፡ |
በማርያ የእገዚአብሔር ቃል ሥጋ ሆነ፡፡ |
ዳዊትና ከእርሱ ጋር የነበሩ እስራኤላውያን የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት ሊያመጡ በይሁዳ ወደሚገኘው ወደ በዓላ ሄዱ፡፡ |
ማርያም በተራራማው በይሁዳ አገር ወዳለችው ከተማ በፍጥነት ተነሥታ ሄደች፡፡ |
ደዊትና እስራኤለውያን በሙሉ ኀይላቸው በመዘመር በእግዚአብሔር ፊት ደሰት አደረጉ፡፡ |
ኤልሳቤጥ የማርያምን የሰላምታ ቃል በሰማች ጊዜ በማሕፀንዋ የነበረው ህፃን ዘለለ፡፡ ኤልሳቤጥም ድምፅዋን ከፍ አድርጋ ተናገረች፡፡ |
እግዚአብሔር በቁጣ ተነሳስቶ ዑዛን በመግደሉ ዳዊት እግዚአብሔርን ሰለፈራ ‹‹እንዲህ ከሆነማ የቃል ኪዳኑን ታቦት እንዴት ልወስደው እችላለሁ?›› አለ |
ኤልሳቤጥ እንዲህ አለች፤ ‹‹የጌታዬ እናት ልትጎበኘኝ መምጣትዋ ለኔ እንዴት ያለ ታላቅ ክብር ነው! |
የእግዚአብሔር የቃል ኪዳን ታቦት የዖቤድኤዶም ቤት ሦስት ወር ተቀመጠ፤ እግዚአብሔርም ዖቤድኤዶምንና ቤተሰቡን ባረከ፡፡ |
እናታችን ማርያም ከኤልሳቤጥ ጋር ሦስት ወር የህል ከቆየች በኋላ ወደ ቤትዋ ተመልሳ ሄደች፡፡ |
እናታችን ማርያም ስላመነች ተባረከች
ኢየሱስ፤ ‹‹ ›› (ሉቃ 11፡ 28)
በዚህ ንግግሩ ኢየሱስ እናቱን ዝቅ አድርጎል ማለት ነው ወይ? በዚህ ንግግሩ ኢየሱስ የእናቱን እውነተኛ ታላቅነት ለመግለፅ ይፈልጋል፡፡ እርሷ በመጀመሪያ አምና የእግዚአብሔርን ቃል ተቀብላ በተግባር ላይ አዋለች፡፡
ማርያም የተባረከችና የኢየሱስ እናት የሆነችው ኢየሱስን ስለጸነሰች ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ያለውን ስላመነችና የሰማዩን አባት ፍቃድም ስለፈጸመች ነው፤ ‹‹አንቺ እግዚአብሔር የተናገረውን ሁሉ የሚፈጽም መሆኑን በማመንሽ ምንኛ የታደልሽ ነሽ››፡፡
ማርያም የመጀመሪያዋ ኢየሱስን የተቀበለች ስትሆን ‹‹እነሆ እኔ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነኝ፤ አንተ እንዳልህ ይሁንልኝ›› በማለት በእሽታና በትህትና መልስ ሰጠችው፡፡
በቤተሰባችን ውስጥ ተስፋ ሊጠፋ በሚጣጣርበት ጊዜ፤ በመስቀሉ ሥር እንኳን በእምነት ጸንታ የቆመችውን ማርያምን ማየት አለብን፡፡ ተስፋዋ በሰዎች ዘንድ በተጠላና በተከዳ ልጇ ላይ ነበር፡፡ በችግሮቻችን መኃል እንኳን የእግዚአብሔርን ፍቅርና የእግዚአብሔርን እውነተኛ ፊቱን ማግኘት እንድንችል እንድትረዳን ማርያምን እንለምናት፡፡
እንጸልይ፡-
አባት ሆይ፣ አንተ የድንግል ማርያምን ልብ ለመንፈስ ቅዱስህ ምቹ መኖርያ ቤት እንድትሆን አዘጋደኃት፡፡በእርሷ ጸሎት እኛም ለክብርህ ብቁ መኖርያ እንድንሆን ታደርገን ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እንለምንሃለን፡፡ አሜን፡፡