እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ለንጽሕና የሚደረግ ተጋድሎ

ለንጽሕና የሚደረግ ተጋድሎ

ጥምቀት ተጠማቂውን ከኃጢአት ሁሉ የመንጻት ጸጋን ይሰጣዋል፡፡ ይሁንና ተጠማቂው ሰው ከስጋዊ ፍላጐቶችና ከተዛቡ ምኞቶች ጋር የሚያደርገውን መንፈሳዊ ተጋድሎ አያቋርጥም በእግዚአብሔር ጸጋም፣

  • ንጽሐ ድንግልና በትክክለኛ ባልተከፋፈለ ልብ መውደድ ያስችለዋልና ተጠማቂው በንጽሕና ድንግልና ስጦታ ይበረታል፡፡
  • እውነተኛውን የሰውን ፍጻሜ በሚሻው የአላማ ንጽሕና ይሆናል በራዕዩ ቀናነት ተጠማቂው ፈቃደ እግዚአብሔርን በሁሉም ነገር ውስጥ ሊሻና ሊፈፅመው ይፈልጋል፡፡
  • በውጫዊውና በውስጣዊው ራዕይ ንጽሕና፣ ስሜቶችንና ምናብን ሥርዓት በማስያዝ ከእግዚአብሔር ትእዛዝ እንድንርቅ ከሚገፋፉን ከጐደፋ ሀሳቦች ጋር ለመተባበር አሻፈረኝ በማለት “አላዋቂን ሰው መልክ ይስበዋል” ሲል መጽሐፉ የተናገረውን ከግምት በማስገባት፡፡
  • በጸሎትም ጭምር መዝለቅ ያሻል፡፡

ራስን መቆጣጠር እኔ በውስጤ መኖራቸውን ካላወቅኋቸው ኃይላት እንማሚመነጭ አስብሁ፡፡ አንተ ካልሰጠኸው በቀር ማንም ቢሆን ራሱን ማቆጣጠር እንደማይችል አለማወቄ … ጅልነት ግሯል፡፡ በውስጣዊ መቃሰቴ ከጆሮህ ደርሶ ሲሆን ኖሮና እኔም ከጥብቅ እምነት ጋር ጭንቀቴን ሁሉ ባንተ ላይ ጥዬ በነበር በእርግጥም ራስን መግዛትን ትሰጠኝ ነበር፡፡

ንጽሕና ራስን የመግዛት ዓይነተኛ አካል የሆነውን ትሕተናን ይጠይቃል፡፡ ትሕትና የሰውን ውስጠት ይጠብቃል፡ ይህም ማለት በምስጥር መጠበቅ የሚገባውን ጉዳይ አለመግለጥ ነው፡፡ በቀላል ስለመጠቃት አለመጠቃቱ ለሚመሠክርለት ለንጽሐ ድንግልናም አገልጋይ ነው፡፡ ትሕትና አንድ ሰው ሌሎችን እንዴት ባለ መንገድ ማየት እንዳለበት፣ ከሰዎች ክብርና ከአንድነታቸው ጋር በሚስማማ መልኩ እንዴት መቀበልና መስተናገድ እንደሚገባው ይመራዋል፡፡

ትሕትና የሰዎችን ምስጢርና ፍቅር ይጠብቃል፡፡ ትሕትና በፍቅር ግንኙነቶች ውስጥ ትእግሥትንና ቁጥብነትን ያጠነክራል፡፡ ትሕትና በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል መከናወን ያለበትን ምሉዕ የእርስ በርስ መሰጣጠት አስፈላጊ የሆነ ሁኔታዎችን መሟላትን ይጠይቃል፡፡ ትሕትና መልካም ፀባይ ነው፡፡ ትሕትና የአለባበስ ምርጫን ይወስናል፡፡ ትሕትና ጤናማ ያልሆነ ጉጉት ስጋት ባለበት ዝምታን ወይም ከመናገር መቆጠብን ያረጋግጣል፡፡ ትሕትና አስተዋይነትም ነው፡፡

የስሜቶች ትሕትና እንዳለ ሁሉ የአካልም ትሕትና አለ፡፡ ትሕትና ለምሳሌ ያህል በአንዳንድ የንግድ ማስታወቂያዎች ላይ ወሲባዊ ስሜትን የሚቀሰቅሱ ትዕይንቶችን ማሳየትን ወይም አንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ውስጣዊ አካልን በማሳየት ረገድ የሚሄዱበትል ያልተገባ ርቀት ይቃወማል፡፡ አዳዲስ አለባበስንና የወቅቱ ርእዮተ ዓለማት የሚያደርሱትን ተጽእኖ ለመቋቋም የሚያስችል የሕይወት መነገድን ይከተሉ ዘንድ ሰዎችን ያነሳሳል፡፡

የትሕትና መልኮች እንደየባህሉ ይለያያሉ፡፡ ነገር ግን ትሕትና በየትኛውም ሥፍራ ቢሆን ለሰው ልጅ የሚገባውን መንፈሳዊ ክብር መረዳት ሆኖ ይገለፃል፡፡ ትሕትና ራስን ከማወቅ ንቃተ ሕሊና ጋር ይወለዳል፡፡ ለልጆችና ለጐልማሶች ትሕትናን ማስተማር ማለት ለሰው ልጅ የሚገባ አክብሮትን በልባቸው መቀስቀስ ማለት ነው፡፡

ክርስቲያናዊ ንጽሕና የማኀበራዊውን ሁኔታ ንጽሕናን ይጠይቃል፡፡ ትሕትና የመገናኛ ብዙኃን የሚያቀርቧቸው ዝርጅቶች አክብሮትንና ቁጥብነትን ግምት ውስጥ የስገቡ እንዲሆኑ ይጠይቃል፡፡ የልብ ንፅሕና ከተስፋፋው የፍትወተ ሥጋ ምኞት ሲያላቅቅ ወሲባዊ ፍላጐትን ከሚያነሳሱና ከማይጨበጡ አይነት የጊዜ ማሳለፊያዎች ይርቃል፡፡

የሥነ ምግባር ቸልተኝነት በመባል የሚታወቀው ሁኔታ በተሳሳተ ነፃነት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ለእውነተኛ ነፃነት እድገት በቅድሚያ ሥነ ምግባራዊ ሕግን ለመማር ፈቃደኛ መሆን ይሻል፡፡ ወጣቶች እውነትን፣ ልባምነትን የሰውን ሥነ ምግባራዊና መንፈሳዊ ክብር የሚጠብቁ እንዲሆኑ መስተማር ያለባቸው መሆኑን መገመት አግባብ ያለው ሀሳብ ነው፡፡

“የክርስቶስ ብስራት (ወንጌል) የወደቀውን ሰው ሕይወትና ባሕል በየጊዜው ያድሳል፤ ሁል ጊዜ የማይጠፉትንመ ከኃጢአት አሳሳችነት የሚመነጩትን ስሕተትንና ክፋትን ይዋጋል፤ ያስወግዳልም፡፡ ወንጌል የሕዝቦችን ግብረ ገብነት ከማንፃትና ወደ ላቀ ደረጃ ከማድረስ አይቦዝንም፤ የሕዝቡንና የየዘመኑን መንፈሳዊ ልዕልናና ስጦታዎች በመውሰድ በላቁ ባህርያዊ ሃብቶች በመጠቀም ከውስጥ እንዲያብቡ ያደርጋቸዋል፤ በክርስቶስ ያበረታቸዋል ፍጹም የደርጋቸዋል፤ ወደነበሩበትም ይመልሳቸዋል፡፡”

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት