እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የልብ ድኽነት

የልብ ድኽነት

ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እርሱን ከምንም ነገርና ከማንም አስበልጠው በእንዲመርጡት ይመክራቸዋል፤ ለእርሱና ለወንጌል ሲሉም “ያላቸውን ሁሉ  እንዲተው” ያዛቸዋል፡፡ ከሕማማቱ ጥቂት ቀደም ብሎ አንዲት የኢየሩሳሌም መበለት ሴትን ምንም ደኻ ብትሆን፣ ያላትን በሙሉ መስጠትዋን በርአያነት አቅርቦላቸዋል፡፡ ወደ መንግሥተ ሰማይ ለመግባት ከሃብት የመራቅን ትእዛዝ መቀበል ግዴታ ፡፡

ክርስቲያን ምእመናን “ፍፁም ፍቅርን የመሻት ጉዟቸው በምድራዊ ነገሮች ጥቅምና ወንጌላዊነት ከሚጠይቀው የድህነት መንፈስ በተፃራሪ በቆመው ሃብትን በማሳደድ ፍላጐት እንዳይደናቀፍ መውደዳቸውን በተገቢው አቅጣጫ መምራት አለባቸው፡፡”

“በመንፈስ ድኾች የሆነ ብፁዓን ናቸው፡፡” ማቴ. 5፡3 ብፅዕናዎች የደስታና የጸጋ፣ የውበትና የሰላም ሥርዓትን ይገልጻሉ፡፡ ኢየሱስ የእግዚአብሔር መንግሥት የእነርሱ የሆነውን ድሆች ደስታ ያከብራል፡፡

ቃል ሰው በሙሉ ፈቃደኛነት የሚቀበለውን ትህትና “የመንፈስ ድኽነት” የሚል ስያሜ ሰጥቶታል፡፡ ሐዋርያም “ለእናንተ ሲለ ድኻ ሆነ” በማለቱ የእግዚአብሔር ድኻነት በምሣሌነት ያቀርባል፡፡

ጌታ በሃብታሞች ያዝናል፤ ምክንያቱም የእነርሱ መጽናኛ የሀብታቸው ብዛት ነውና፡፡ “ትእቢተኛ ምድራዊ ሥልጣንን ይሻል፡፡ በመንፈስ ድኾች የሆኑትን ግን መንግሥተ ሰማያት የእነሱ ናትና ብፁዓን ናቸው፡፡”  ሁሉንም ነገር በሰማይ ላለው አባት መተው ይገባል ምክንያቱም ለነገ ከመጨነቅ ነፃ የሚያወጣ እርሱ ነውና፡፡ እግዚአብሔርን ማመን ለድሆች ብፅዕና የሚያስፈልግ ዝግጅት ነው፡፡ እነርሱ እግዚአብሔርን ያያሉና፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት