እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

፩ - ስምህ ይቀደስ

    ፩ - “ስምህ ይቀደስ”

እዚህ ላይ “መቀደስ” የሚለው ቃል መወሰድ ያለበት በጥሬ ትርጉሙ አለመሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም የሚቀድስ፣ ቅዱስ የሚያደርግ እግዚአብሔር ብቻ ነው፤ የቃሉ አጠቃቀም አንድን ነገር እንደ ቅዱስ ለማወቅ፣ በተቀደሰ መንገድ ለመያዝ በመመዘኛነት የተወሰደ ነው፡፡ ስለዚህ በአምልኮ ረገድ ይህ ልመና አንዳንድ ጊዜ እንደምስጋና አንደ ውዳሴ ሆኖ ይታያል፡፡ ይሁን እንጂ፣ እዚህ ላይ ይህ ልመና ፍላጐትን በቃላት ስለመግለጽ ከኢየሱስ የተማርነው ነው፤ ልመናው እግዚአብሔርና ሰው የሚሳተፉበት ምኞትና ተስፋ ነው፡፡ በዚህ ለአባታችን በማቅረብ የመጀመሪያው ልመና እኛ ከአምላክነቱ ጠልቅ ምሥጢርና የስብዕናችን መዳን ትዕይንት ውስጥ እንገባለን፡፡ ስሙ ይቀደስ ዘንድ አብን መማጸናችን በዘመን ፍፃሜ ወደሚሆነው ፍቅር የተመላ ቸርነቱ “በክርስቶስ ለማድረግ እንደወደደ” “በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን እንሆን ዘንድ” ኤፌ 1፡9 ይስበናል፡፡

እግዚአብሔር በእቅዱ ወሳኝ ጊዜአት ውስጥ ስሙን ይገልጣል፡፡ ነገር ግን እርሱ ይህን የሚያደርገው ሥራውን ወደ ፍጻሜ በማድረስ ነው፡፡ ሆኖም ይህ ሥራ ስለእኛና በእኛ ውስጥ እውን የሚሆነው ስሙ በእኛና በእኛም አማካይነት ስሙ ሲቀደስ ብቻ ነው፡፡

የእግዚአብሔር ቅድስና የዘላለማዊ ምስጢሩ የማይደረስበት ውስጠት ነው፡፡ በፍጥረትና በታሪክ የተገለጸውን የዚሁን ውስጠት ክፍል ቅዱስ መጽሐፍ “ክብር” የጌትነቱ የግርማ ሞገሱ ብርሃን ይለዋል፡፡ እግዚአብሔር ሰውን በመልኩና በአርአያው በመፍጠር “የክብርና የምስጋና አክሊል ጫነለት፣” ነገር ግን ሰው ኃጢአት በመሥራቱ “የእግዚአብሔር ክብር ጐድሎታል፡፡” ከዚያን ወዲህ ሰውን ወደቀድሞው የፈጣሪ አምሳልነቱ ለመመለስ እግዚአብሔር ስሙን በመግለጥና በመስጠት ቅድስናውን ይገልጣል፡፡ቆላ 3፡1ዐ

እግዚአብሔር ለአብርሃም በሰጠው ተስፋና ከዚያም በገባለት መሐላ ስሙን ሳያሳውቅ ቃል ይገባል፡፡ እግዚአብሔር ስሙን መግለጽ የሚጀምረው ለሙሴ ሲሆን ከግብጻውያኑ ባዳናቸውም ወቅት “በክብሩ ከፍ ከፍ ብሎአልና፤” በመላው ሕዝብ ፊት እንዲታወቅ ያደርገዋል፡፡ በሲና ተራራ ላይ ከተከናወነው ቃል ኪዳን በኋላ ይህ ሕዝብ “የእርሱ ነው” ስለዚህም “ቅዱስ” ወይም “የተቀደሰ” ሕዝብ መሆን አለበት፤ /ቃሉ በእብራይስጥ ሁለቱንም ያሰማል/ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ስም በዚሁ ሕዝብ ውስጥ ይኖራልና፡፡

ቅዱስ አምላካችው በተደጋጋሚ “እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ቅዱስ ነኝና እናንተ ቅዱሳን ሁኑ፡፡ የሚል የተቀደሰ ሕግ የሚሰጣቸው ቢሆንም፣ ስለስሙም ጌታ ትእግስትን ቢያሳይም ሕዝቡ ከእሥራኤል ቅዱስ ፊቱን በመመለስ በአሕዛብ መካከል ስሙን አርክሷል” በዚህም ምክንያት የብሉይ ኪዳን ጻድቃን ከስደት የተመለሱ ድኾችና ነቢያት በስሙ ፍቅር የተቃጠሉ ነበሩ፡፡

በመጨረሻም የቅዱስ እግዚአብሔር ስም በሥጋ፣ በአዳኝነቱ በእርሱነቱ መገለጥ፣ በቃሉና በመሥዋዕቱ በኢየሱስ የተገለጠልን፤ ተሰጠንም፤ እርሱ ይህን ስም የገለጠው፣ በሥራዎቹ፣ በቃላቱና በመስዋዕቱ ነው፡፡ የክህነታዊው ጸሎቱ እምብርትም “ቅዱስ አባት … እነርሱን ደግሞ በእውነት የተቀደሱ እንዲሆኑ እኔ ራሴን ስለ እነርሱ እቀድሳለሁ የሚለው ቃሉ ነው፡፡” ዮሐ 17፡11፤19 ምክንያቱም እርሱ ስሙን “ይቀድሳል”፤ የአብንም ስም ይገልጥልናል፡፡ በክርስቶስ ፋሲካ ማብቂያ ላይ አብ “ከስምም ሁሉ በላይ የሆነውን ስም ይሰጠዋል፤ “ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ ነው፡፡” ፊሊሞና 2፡9-11

“በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስምና በአምላካችን መንፈስ በጥምቀት ውሃ ታጥበናል… ተቀድሰናል… ጸድቀናልም፡፡” 1ቆሮ 6፡11 አባታችን በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ወደ ቅድስና ይጠራናል፡፡ እርሱ “ለእኛ ከእግዚአብሔር የተገኘ ጥበብ፣ እና … ቅድስና በሆነው በክርስቶስ ኢየሱስ ለሆነው ሕይወታችን መገኛ” 1ቆሮ 1፡3ዐ፤ 1ተሰ 4፡7 ነውና ክብሩና ሕይወታችን በእኛ ውስጥና በእኛም አማካይነት የሚሆነው የሰሙ ክብር ይወሰናል፡፡ የመጀመሪያው ልመናችንም አስፈላጊነት ይህ ነው፡፡

“እርሱ ብቻ ቀዳሽ ሆኖ ሳለ፣ እርሱን ሊቀድሰው የሚችል ማነው? ነገር ግን እርሱ ራሱን “እኔ እግዚአብሔር ቅዱስ ነኝና … ለእኔም ትሆኑ ዘንድ ከአሕዛብ ለይቻችኋለሁና ቅዱሳን ትሆኑልኛላችሁ” ሌዋ 2ዐ፡26 እንዳለው እና በምስጢረ ጥምቀት የተቀደስን መሆን የጀመርነውን በጽናት እንድንቀጥልበት እንሻለን፤ እንጠይቃለንም፡፡ ይህንንም በየዕለቱ እንለምናለን በየዕለቱ የምንወድቀው እና ያለማቋረጥ በመቀደስ ኃጢአቶቻችንን ለማንጻት ዕለት በዕለት መቀደስ ያሻናልና … ይህ መቀደስ በውስጣችን ይዘልቅም ዘንድ እንጸልያለን፡፡

በአሕዛብ መሐከል የእግዚአብሔርን ስም መቀደስ የማይነጣጠል ሁኔታ፤ በሕይወታችንና በጸሎታችን ላይ የተመሠረተ ነው፡፡

በቅድስናው ፍጥረትን ሁሉ የሚያድን የሚቀድስ ስሙን እግዚአብሔር ይቀድስ ዘንድ እንለምነዋለራ፡፡ ለጠፋው ዓለም ምሕረትን የሚያደርግ ይህ ስም ነው፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሔር ስም በእኛ ውስጥ በድርጊቶቻችን እንዲቀደስ እንለምናለን፡፡ ምክንያቱም እኛ መልካም ሕይወት ስንኖር የእግዚአብሔር ስም ይባረካል፤ በክፋት ስንኖር ግን ስሙ ይሰደባል፡፡ ሐዋርያው እንደሚለው “በእናንተ ሰበብ የእግዚአብሔር ስም በአሕዛብ መካከል ይሰደባል፡፡” ስለዚህም የአምላካችን ስም ቅዱስ እንደሆነ ሁሉ እኛም ደግሞ በነፍሳችን ቅድስናን እናገኝ ዘንድ እንለምናለን፡፡

“ስምህ ይቀደስ” ስንል በእርሱ ውስጥ በሆንን በእኛ ዘንድ እንዲቀደስ እንለምናለን እንደዚሁም ገና የእግዚአብሔር ጸጋ ለሚጠባበቃቸው ሌሎች ሰዎችም እንለምናለን፡፡ ይህንንም የምናደርገው ለሁሉም፣ ለጠላቶቻችንም እንኳን ሳይቀር እንድንጸልይ የሚጠይቀንን ትእዛዝ ለመፈጸም ነው፡፡ “ስምህ በእኛ ውስጥ ይቀደስ” የማንለው፡፡ በሰዎች ሁሉ ዘንድ እንደዚሁ እንዲሆን እንለምናለነና፡፡”

ህ ልመና ሌሎቹን ሁሉ ያጠቃልላላ፡፡ እደተከታዮቹ ስድስት ልመናዎች በክርስቶስ ጸሎት ፍጻሜን ያገኛል፡፡ በኢየሱስ ስም ከተጸለየ ለአባታችን የሚቀርብ ጸሎት የእኛ ጸሎት ነው፡፡ ኢየሱስ በክህነታዊ ጸሎቱ “ቅዱስ አባት ሆይ፣ እነዚህን የሰጠኸኝን በስምህ ጠብቃቸው” ዮሐ 17፡11 ሲል ይለምናል፡፡

/የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ትምህርተ ክርስቶስ ከቁጥር 2807-2815/

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት