እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ባዶ!? ከባዶ ወደ ማዶ!

Easter 2012 webpageባዶ!? ከባዶ ወደ ማዶ!

"ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን መግደላዊት ማርያም ገና ጨለማ ሳለ ማለዳ ወደ መቃብር መጣች ድንጋዩም ከመቃብሩ ተፈንቅሎ አየች።"

(የዮሐንስ ወንጌል 20:1)

የክርስቶስ መቃብር ባዶ ሆኖ መታየትና መገኘት ለአማኞች የእርሱን ሕያውነት ያመለክታል። ክርስቶስ ከመቃብር በላይ ነው። በውስጣችንም ሆነ በውጫዊ ነገር ባዶነት ሲሰማን ራመድና ቀና ብለን በክብር ያለውን ክርስቶስን እንድናይ እንጋብዛለን።

"ገብተውም የጌታን የኢየሱስን ሥጋ አላገኙም። እነርሱም በዚህ ሲያመነቱ፥ እነሆ፥ ሁለት ሰዎች የሚያንጸባርቅ ልብስ ለብሰው ወደ እነርሱ ቀረቡ፤ ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው። ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።" (የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 24:3-5)

ምናልባት ዘንድሮ እኛ ባሰብነውና በፈቀድነው መልኩ የትንሣኤ በዓልን ሳናከብር ስንቀር ውስጣችን ባዶነት ቢሰማውም የክርስቶስን ሕያውነት በልዩ መልኩ እንድናገኝ ከመጋበዝ ውጪ ባዶነት መገለጫችን አይደለም፣ የክርስቶስ መቃብር ባዶነት ለክርስቲያኖች የእርሱ መነሣት መልእክትን ነው የሚያስተላልፈው። እንዲሁም ትንሣኤን በምናከብርበት መሰዋዕተ ቅዳሴ የምእመናን ወንበሮቻችን ባዶ ሆነው ቢታዩም በእምነት ዓይን የመገኘታችሁን መልእክት ያስተላልፋሉ፣ ክርስቶስ ሕያው ነውና ክርስቲያኖችም ሕያዋን ነን።

መቃብሩ ባዶ ሆኖ መታየቱ ለሊቀ ለካህናቱና ፈሪሳውያኑ የክርስቶስ አስክሬን ተሰረቀ ብለው ለማውራት ምክንያት ሲሆናቸው ለማርያም መግደላዊት፣ ለማርያም ሰሎሜ፣ ወደ መቃብሩ ለሮጡት ሁለቱ ደቀመዛሙርት፣ እንዲሁም በዘመናት ለነበሩትና ዛሬም ላለነው ለእኛ ባዶ መቃብር የክርስቶስን ሕያውነት ያስተጋባል።

መልካም በእምነት፣ በፍቅርና በተስፋ የተሞላ የትንሣኤ በዓል ለሁላችን!

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት