እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የሰው ልጅ ፍጥረት

God-Adam

የሰው ልጅ ፍጥረት


እግዚአብሔር በመጀመሪያ ሰውን በአርአያውና በአምሳሉ ፈጠረው፡፡ ዘፍ.1፡26-27፡፡

እግዚአብሔር ፡-

  • ዘላለማዊ ነው
  • አእምሮ አለው፤ እንዲያውም ራሱ አእምሮ ነው፡፡
  • ፍጹም ፈቃድ አለው
  • ልብ አለው፤ ያውም  ራሱ ፍቅር ነው፡፡

እግዚአብሔር ሁሉንም ነገሮች ያለው  በምልአት ነው፤ ሰው ግን ፍጡር እንደመሆኑ መጠን በመለኮታዊ ባሕርያት ውስጥ መሳተፍና መቀበልም የሚችለው በፍጥረት አቅም መጠን ብቻ ነው፤ ስለሆነም ማንኛውም ነገር ማለትም በሰው ቋንቋ ስለ እግዚአብሔር የሚባለው ሁሉ ትንሽ ለማመሳሰል ያህል ነው እንጂ በተመሳሳይና በበቂ ደረጃ ማስቀመጥ አይቻልም፡፡ ለምሳሌ እግዚአብሔር ዓይን አለው ስንል ቶሎ ብሎ ወደ አእምሮአችን የሚመጣው የራሳችን /የሰው/ዐይን ነው፤…ያ ደግሞ ብዙ ጉድለት አለበት፤ ስለዚህ ስለእግዚአብሔር ስናስብ፣ ስንናገርና ስንገልጽ ማስተዋል ይጠበቅብናል ማለት ነው፡፡


ስለዚህ ሰው ዘላለማዊ ነው ስንል መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ የለውም ማለታችን ነው እንጂ ልክ እንደ ፈጣሪው ነው ማለት አይቻልም፤ በእርግጥ ነገሮች ሁሉ ከሰው ልጆች አእምሮ በላይ ናቸው። ማለትም የሰውን ከ…እስከ…ማብራራት አይቻለንም፤ ለምሳሌ ያህል ሰውን ራሱን ስንወስድ አምላክ እሱን መቼ እንዳሰበውና እንዲኖርም እንደወሰነው፤ መለኮታዊ ስጦታውና ታላቅነቱ ምን ያህል እንደሆነ… ማንም አያወቅም፤ ሆኖም ግን ሰው ዘላለማዊ መሆኑን ማንም ሊጠራጠር አይችልም፡፡ የሰው ልጅ የዘላለማዊነት ባሕርይ ነጻ የፈጣሪ ስጦታ (ጸጋ) እንጂ ከራሱ የተፈጥሮ ባህርይ የሚመነጭ/የመነጨ/ አይደለም፡፡


ይህንን ራሱ ክርስቶስ በግልጹ አስቀምጦታል፤…. እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ…የሐ.6፡5።

በሌላ በኩልም ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ በማለት ይናገራል፤ እግዚአብሔር ዓለምን እጅግ ስለወደደ አንድያ ልጁን ሰጠ፤….ዮሐ.3፡16፡፡


ሐዋርያ ጳውሎስም ይህንኑ በሚያሰገርም ሁኔታ ይገልጻል እንዲህ ሲል፤ በሰማይ መንፈሳዊ በረከትን በመስጠት በክርስቶስ  የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እግዚአብሔር አባት የሆነው አምላክ ይመስገን፡፡ ቅዱሳንና ነቀፋ የሌለብን ሆነን በፊቱ እንድንገኝ፤ ዓለም ሳይፈጠር በክርስቶስ መረጠን፡፡ ኤፌ.1፡3-4፡፡


የክርስቶስ ሰው መሆን በራሱ ሰው ዘላለማዊ ዋጋ ያለው ለመሆኑ የመጀመያርውና የማያዳግም ማስረጃ ነው፤ ማለትም ክርስቶስ ሰው የሆነውና በሰው ልጆችም ታሪክ ውስጥ ለመጋባት የፈለገውና የተትረፈረፈ ሕይወት እንዲያገኙ… ነው ያለው ያም ሕይወት እሱ ራሱ እንደሆነና ያንንም ሕይወት የሚኖር ዘላለማዊ መሆኑን ለማሳየት ነው፡፡ዮሐ.10፡6፡፡


ክርስቶስ ወደ ዓለም የመጣው እንዲሁ ለጊዜያዊ ነገር ብቻ ቢሆንማ ኖሮ ምንም አያስገርምም ነበር፤ ምክንያቱም ሞቶ ከሞት ያስነሣቸውም ሰዎች ተመልሰው ሞተዋል ማቱሰላም ምንማ ያህል ረጅም ዕድሜ ቢሰጠውም ሞት አልቀረችለትም፤ እንዱሁም ዓለም እስከምታልቅ ድረስ እያንዳንዱን ሰው ከሞት ካስነሣ በኋላ ሁሉም ተመሳሳይ ዕድል ተሰጥቶአቸው ከዚያ በኋላ ሁሉም አለቀ… ሆኖ በቀረ ነበር ማለት ነው፡፡


እንደዚህ እንዳልሆነ ነው ቅድስት ቤተክርስቲያንም እንዲህ በማለት የምታስተምረን:-

ማን ፈጠረን? - እግዚአብሔር፡፡

ለምን ፈጠረን? - እንድናውቀው፤ እንድንወደው፤ ትእዛዙንም ፈጽመን/ጠብቀን/ መንግሰተ ሰማይ እንድንገባ፡፡

የሰው ፍጻሜዎች ስንት ናቸው? - አራት ናቸው እነሱም፡-

ሞት፤ ፍርድ፤ ገሃነመ እሳት፤ መንግሥተ ሰማያት፡፡

እንግዲያውስ ያ መንግሥተ ሰማያት የሚባለው ነው ዘላለማዊ ነው የምንለው፡፡ ዘላለማዊ ማለትም

ራሱ የእግዚአብሔር ሌላ ስሙ ማለት ነው፡፡

ስለዚህ የሰው ልጅ የመጨረሻው ደሞዙ ምንድነው ከተባለ እግዚአብሔር ራሱ ነው ማለት ነው፡፡

ያንን ደመወዝ አለማግኘት እንግዲህ ምንና ምን ያህል ኪሳራ መሆኑን የሚያውቅና የሚሠራ እንዴት ያለ ጥበበኛ ነው ማለት ይቻል ይሆን! ስለመፈጠሩ ማወቅን ችላ ብሎ፣ ፈጣሪውን እያወቀ እንዳላወቀ መሆንስ … ምን ዓይነት ዕድል ሊሆን ይችላል? ያላወቀ እውነትም አላወቀም ነው፤ ያወቅነውስ?

ሰው ክቡር መሆኑን አላወቀም እንስሳንም መሰለ ይላል ቃለ እግዚአብሔር፡፡


አባ ገብረወልድ ወርቁ - ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን። አዲስ አበባ

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት