እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

4- የትኞቹ መጽሐፍ የመጽሐፍ ቅዱስ አካል እንደሆኑ በምን እናውቃለን?

4. የትኞቹ መጽሐፍ የመጽሐፍ ቅዱስ አካል እነደሆኑ በምን እናውቃለን?

የተለያዩ አሳታሚዎች ጥንታዊ ጽሑፎችን ከፊታችን በማቅረብ የተረሱ የወንጌል ተግባራትን እንደያዙ የኢየሱስን ቀሪ ሥራዎች እንደሚዘክሩ እውነተኛ መጽሐፍት አድርገው በሚያቀርቡበት ዓለማችን ውስጥ የምንሰማው ተደጋጋሚ ጥያቄ ነው፡፡ የቶማስ ወንጌል፣ የይሁዳ ወንጌል፣ የፊልጶስ ወንጌል፣ የሚባሉትን ጥንታዊ መጽሐፍት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያልተካተቱትን ለምንድነው? በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ መካተት ያለበትን እና መካተት የሌለበትን የሚወስነው ማነው?

ሐዋርያት መጽሐፍ ቅዱስን እንደ ቅዱስ ትውፊት አካል እና እንደ እምነት አድርገው ለቤተክርስቲያን አደራ ሰጥተዋል፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን በመንፈስ ቅድስ መሪነት እነዚህን ጽሑፎች በመደበኛው ዝርዝር ለማዋቀር ያለውን አስፈላጊነት ተረዳች፡፡ ይህ የተሟላ የመጽሐፍት ዝርዝር የቅዱሳን መጽሐፍት "ቀኖና" ይባላል፡፡

ቀኖና የሚለው የግሪክ ቃል "ማስመሪያ፣ መለኪያ፣ መሸለጊያ ወይም መመተሪያ" የሚሉትን ትርጉሞች ያሰማል።

በመጀመርያ ጳጳሳት የመጽሐፍቱን ዝርዝር ያዋቀሩት በሃገረ ስብከታቸው ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ግልጋሎት ነበር፡፡ እንደ ዛሬው የማተሚያ ማሽን ባለማመኖሩ አብዛኞቹ አብያተ ክርስቲያናት እና ምዕመናን ሙሉ "መጽሐፍ ቅዱስ" አልነበራቸውም፡፡ መጽሐፍት የሚባዙት እጅግ አድካሚ በሆነው በእጅ የመገልበጥ ሥራ ነበር፤ በዚህም የተነሳ መጽሐፍቱ ዋጋቸው የማይቀመስ እና በጣም ጥቂት ብቻ ነበሩ፤ ከዚህ አንፃር በግል መንፈሳዊነት ንባብ ማድረግ በጥቂት ክርስቲያኖች እጅ ብቻ የሚገኝ ቅንጦት ነበር፡፡ ምእመናን መጽሐፍ ቅዱስን የሚያገኙት በመሥዋዕተ ቅደሴ ውስጥ ሲነበብ በማድመጥ ነበር፡፡ ጥንታዊው ቀኖና በቅዳሴ ላይ ሊነበቡ የሚችሉ መጽሐፍትን ያካተተ ብቻ ነበር፡፡

አልፎ አልፎ ለሚነሱ እንግዳ ይዘት ያላቸው የስህተት "ወንጌላት"ን ለመቃወም ጳጳሳት የመጽሐፍ ቅዱስ ቀኖናን ለማዋቀር ይነሳሱ ነበር፡፡ እነዚህ የተሳሳቱ መጽሐፍት በአንዳንድ የኢየሱስ ሐዋርያት ስም የቀረቡ በመሆናቸው ማጣራት ያስፈልግ ነበር፡፡ ለምሳሌ የአንጾኪያው የመጀመርያ ጳጳስ በጊዜው ይዘወተር የነበረውን "የጴጥሮስ ወንጌል" የሚል መጽሐፍ እንዳይጠቀሙ በእርሱ ሃገረ ስብከት ሥር ያሉትን አብያተ ክርስቲያናት በግልጽ አግዷቸዋል፡፡

ከእነዚህ መጽሐፍት አብዛኞቹ ዛሬም በአርኪዮሎጂ እና በታሪክ አጥኚዎች አማካኝነት በኛ ዘንድ በአዲስ መልክ ብቅ ብለዋል፡፡ ሊቃውንት እና የቤተክርስቲያን ወገኖች "አፖክሊፋ" ብለው ይጠራቸዋል፤ በግሪኩ ስያሜ "የተደበቁ" ማለት ሲሆን የዚህ ምክንያት እነዚህ መጽሐፍት በቤተ ክርስቲያን ዘንድ ተቀባይነት በማጣታቸው ነው፡፡ የመገናኛ ብዙኅን ያለ እረፍት የሚያሞካሿቸው ቢሆኑም ተአማኒነት የጐደላቸው ጽሑፎች ናቸው፤ ብዙዎቹ ጽሑፎች ወንጌል ከተፃፈ ከረጅም ጊዜ በኋላ የተፃፉ፣ በይዘታቸው ወጥ ወይም ቀጥ ያለ ዘውግ ያላቸው እና ለተራ ንባብ የተፃፉ ናቸው፡፡ እነዚህ በቤተክርስቲያን ሕጋዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ቀኖና ውስጥ ያልተካተቱባቸው አያሌ አሳማኝ ምክኒያቶች አሉ፡፡

የተለያዩ የቀኖና ዝርዝሮች ከጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያዎቹ ክፍል ዘመናት እንስቶ ቀርበዋል፡፡ በ367 ዓ.ም ቅዱስ አቴናሲዮስ የአዲስ ኪዳን የቀኖና መጽሐፍት ልክ ዛሬ ያሉትን ዓይነት እንደሆኑ አረጋግጧል፡፡ የተለያዩ ጳጳሳት በሂፖ ጉባኤ /393 ዓ.ም/ እና በካርቴጅ ጉባኤ /በ397 ዓ.ም/ ላይ ይህንኑ የቀኖና ዝርዝር አጽድቀዋል፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍት የመጨረሻው የቀኖና ዝርዝር የጸደቀው በአራተኛው ክፍለ ዘመን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የሮም በጠሩት ጉባኤ ላይ ነው፡፡

ነገር ግን ደግመው የምንመሰክረው ነገር ቢኖር እነዚህ የተለያዩ ጉባኤያት ያጸደቁት ነገር አስቀድመሞ ከሐዋርያት እጅ በአደራ የተቀበሉትን እና በቤተ ክርስቲያን የተቀደሰው ትውፊት ጠብቆ ያቆየላቸውን ልማድና እምነት ነው፡፡

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት - ብሉይና አዲስ ኪዳናት 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት