እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ጸሎታችን አልተሰማም ብለን ለምን እናማርራለን?

ጸሎታችን አልተሰማም ብለን ለምን እናማርራለን?

በመጀመሪያ ደረጃ በዚህ ሁኔታ መገረም ይገባናል፡፡ ለሰጠን ሁሉ ባጠቃላይ እግዚአብሔርን ስናወድስ ወይም ስናመሰግን ጸሎታችን በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት ይኑረው ወይም አይኑረው እምብዛም አንጨነቅም፤ በሌላ በኩል ደግሞ የልመናዎቻችንን ውጤቶች ማየት እንሻለን፡፡ ጸሎታችንን የሚያነቃቃው የእግዚአብሔር አምሳል ምንድን ነው? መጠቀሚያ መሣሪያ ነውን? ወይስ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት?

"እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገባን" ሮሜ 8፡26 አለማወቃችንን አምነናልን? እግዚአብሔርን የምንለምነው "ለእኛ የሚጠቅመንን ነው"? "እኛ ከመለመናችን በፊት አባታችን የምንፈልገውን ያውቃል"፣ ማቴ. 6፡8 ነገር ግን ልመናችንን ይጠብቃል፣ ምክንያቱም የልጆቹ ክብር የተመሠረተው በነፃነታቸው ላይ ነውና፡፡ ስለዚህ የሚፈልገውን ነገር በእርግጥ ማወቅ እንችል ዘንድ ከእርሱ የነፃነት መንፈሰ ጋር አብረን መጸለይ አለብን፡፡ ሮሜ.8፡27

ለምቾታችሁ ታውሉት ዘንድ በክፋ ትለምናላችሁና አትቀበሉም በተከፋፈለ ልብ ከጸለይን፣ እኛ "አመንዝራዎች" ነን፤ የሚመኝልን ደህንነታችንን፣ ሕይወታችንን ነውና እግዚአብሔር ሊሰማን አይችልም፡፡ "ወይስ መጽሐፍ በእኛ ዘንድ ያሳደረው መንፈስ በቅንዓት ይመኛል ያለው በከንቱ እንደተናገረ ይመስላችኋል?" ያዕቆብ 4፡5 እግዚአብሔር ለእኛ "ቀናተኛ" መሆኑ የፍቅሩን እውነተኛነት የሚያሳይ ምልክት ነው፡፡ ወደ መንፈስ ቅዱስ ፍላጐት ከገባን ጸሎታችን ይሰማል፡፡

እግዚአብሔር ይሰጥህ ዘንድ የለመንከውን ነገር ወዲያውኑ ባለመግኘትህ አትጨነቅ፤ ምክንያቱም አንተ ጸሎትህን ሳታቋርጥ ከእርሱ ጋር በቆየህ መጠን ከጠየቅኸው የበለጠም ሊሰጥህ ይፈልጋልና፡፡

Evagrius Ponticus, De oratione

እርሱ ያዘጋጀልንን ነገር መቀበለ እንድንችል ዘንድ እግዚአብሔር ፍላጐታችን በጸሎት እንዲገለጽ ይሻል፡፡

St. Augustine

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት