የኢየሱስ የጸሎት ሰዓት
- Category: ስለ ጸሎት
- Published: Friday, 13 April 2012 10:20
- Written by Super User
- Hits: 3437
- 13 Apr
የኢየሱስ የጸሎት ሰዓት
"ሰዓቱ" በደረሰ ጊዜ ኢየሱስ ወደ አብ ጸለየ፡፡ በወንጌል የሰፈነው እጅግ ረጅሙ ጸሎት መላውን የፍጥረትን የድኅንነትን ሥራ እንዲሁም ሞቱንና ትንሣኤውን ያጠቃልላል፡፡ ልክ ፋሲካው "ለአንዴና ለሁሌም" በቤተክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ ውስጥ እንደሚኖር ሁሉ የኢየሱስ የመጸለያ ሰዓትም ሆኖ የእርሱ ይዘልቃል፡፡
ክርስቲያናዊ ትውፊት ይህንን ጸሎት የኢየሱስ "ክህነታዊ" ጸሎት በትክክል ይጠራዋል፡፡ ይህ ጸሎት ከመሥዋዕቱ ሙሉ ለሙሉ ወደ "ተቀደሰለት" ወደ አብ ከማለፉ ከፋሲካዋ ጋር የማይነጣጠል የሊቀ ካህናችን ጸሎት ነው፡፡
በዚህ ፋሲካዊና መስዋዕታዊ ጸሎት ሁሉም ነገር በክርስቶስ ይጠቃለላል፡፡ አምላክና ዓለም፣ ቃልና ሥጋ፣ ዘላለማዊ ሕይወትና ጊዜ፣ ራስን አሳልፎ የሚሰጥ ፍቅርና እሱን የሚክደው ኃጢአት፤ ያላት ደቀ መዛሙርትና እነርሱን በመስማት በኢየሱስ የማያምኑ ሰዎች፤ ውርደትንና ክብር ከዚህ ውስጥ የሚካተቱ ናቸው፡፡ ይህ ጸሎት የአንድነት ጸሎት ነው፡፡
ኢየሱስ የአብን ሥራ ሙሉ በሙሉ ፈጽሟል፤ ጸሎቱ እንደ መስዋዕቱ እስከ ጊዜ ፍጻሜ ይደርሳል፡፡ የዚህ ሰዓት ጸሎት በፍፃሜ ዘመናትን ይመስላል፣ ወደ ፍጻሜአቸውም ያደርሳቸዋል፡፡ አብ ሁሉን ነገር የሰጠው ልጁ ኢየሱስ፣ራሱን ሙሉ በሙሉ መልሶ ለአብ አስረክቦአል፤ ይሁን እንጂ አብ በሥጋ ላይ ሁሉ በሰጠው ሥልጣን በታላቅ ነፃነት ራሱን ይገልፃል፡፡ ራሱን አገልጋይ ያደረገ ወልድ ሁሉን የሚችል ጌታ ነው፡፡ ስለእኛ የሚጸልየው ሊቀ-ካህናት በውስጣችን የሚጸልየው ጸሎታችንንም በሚሰማው እግዚአብሔር ነው፡፡
ወደ ጌታ ኢየሱስ ቅዱስ ስም በመግባት "አባታችን ሆይ" ሲል የሚያስተምረንን ጸሎት በልባችን መቀበል እንችላለን፡፡ ክህነታዊው ጸሎቱ ከውስጥ በሚመነጭ ሁኔታ የአባታችን ሆይን ታላቅ ልመና፣ ለአብ ስም የሚኖር መቆርቆርን፤ ለመንግሥቱ ክብር የሚኖር የላቀ ቀናኢነትን የአብ ፈቀድና የድኅንነት እቅዱ መፈጸም፤ እንዲሁም ከክፋት ነፃ መሆንን ከፍፃሜ ያደርሳል፡፡
በመጨረሻ በዚህ ጸሎት ኢየሱስ የጸሎት ሕይወት ዋኛ ምስጢር የሆነውንና የማይነጣጠለውን የአብና የወልድን "ዕውቀት" ይገልጥልናል፤ ይሰጠናልም፡፡
ምንጭ፡ የካቶሊክ ትምህርት ክርሰቶስ - ቁጥር 2725-2751