እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

6 - አታመንዝር

ስድስተኛይቱ ትእዛዝ

“አታመንዝር” ዘጸ. 2ዐ፡14፤ ዘዳ. 5፡18

“አታመንዝር” እንደተባለ ሰምታችኋል፡፡ እኔ ግን እላችኋለሁ፤ ወደ ሴት ያየ ሁሉ የተመኛትም፣ ያን ጊዜ በልቡ ከእርስዋ ጋር አመንዝሯል፡፡ ማቴ. 5፡ 27-28

“ወንድና ሴት አድርጐ ፈጠረው …”

“እግዚአብሔር ፍቅር ነው፤ በራሱም የአንድነትና የፍቅር ምስጢር ሆኖ ይኖራል፡፡ እግዚአብሔር በአምሳያው የሰውን ዘር ሲፈጥር … በወንድና በሴት ባሕርይ ላይ ጥሪን ቀረጸ፤ በዚያም መሠረት የፍቅርና፣ የአንድነት አቅምና ኃላፊነት ሰጣቸው፡፡”

“እግዚአብሔር ሰውን በመልኩ ፈጠረ… ወንድና ሴት አድርጐ ፈጠራቸው፡፡” ዘፍ.1፡27 “ብዙ ተባዙ ምድርን ሙሏት” ዘፍ. 1፡28 ብሎ ባረካቸው፡፡ “እግዚአብሔር አዳምን በፈጠረ ቀን በእግዚአብሔር ምሳሌ አደረገው፣ ወንድና ሴት አድርጐ ፈጠራቸው፤ ባረካቸው፣ ስማቸውንም በፈጠረበት ቀን አዳም ብሎ ጠራቸው፡፡”

ጾታዊ ባህርይ በሰው አጠቃላይ ገጽታ፤ በሰው አካልና ነፍስ ባለው አንድነት ላይ በሁሉ አንፃር ከፍ ያለ ተጽእኖ አለው፡፡ ጾታዊ ባህርይ በተለይ የፍቅር ስሜትን፣ የመዋደድና የመውለድ ችሎታን፣ እንደሁም በጠቅላላ ሲታይ ደግሞ ከሌሎች ጋር ትስስር የመፍጠርን ተሰጥዎ ያመለክታል፡፡

ወንድም ይሁን ሴት ማንኛውም ሰው ፆታዊ ማንነቱን ማወቅና መቀበል አለበት፡፡ አካላዊ፣ ሥነ ምግባራዊና መንፈሳዊ ልዩነት እንዲሁም መደጋገፍ የተቃኙት የጋብቻን ስኬታማነት እና የቤተሰብን ሕይወት ማበብ እንዲያስገኙ ነው፡፡ የባልና የሚስት እንደሁም የሕብረተሰብ ስምምነት (መግባባት) በከፊል የሚመሠረተው የሁለቱ ጾታዎች መደጋገፍ፣ ፍላጐቶችና መተባበር በሚተገበሩባቸው ሁኔታዎች ላይ ነው፡፡

“እግዚአብሔር ሰዎችን ወንድና ሴት አድርጐ ስለፈጠራቸው፤ ለመንድና ለሴት እኩል የሆነ ግላዊ ክብርን ይሰጣል፡፡” “ወንድና ሴት በእግዚአብሔር መልክና አምሳያ የተፈጠሩ ስለሆኑ ወንድ ሰው ነው፤ እንዲሁም ሴት ከወንድ ጋር እኩል የሆነች ሰው ናት፡፡”

ዓይነቱ አንድ ባይሆንም እኩል የሆነ ሰብአዊ ክብር ያላቸው ሁለቱም ጾታዎች የእግዚአብሔር ኃይልና ርኀራኄ አምሳሎች ናቸው፡፡ በጋብቻ አማካይነት የሚፈጸመው የወንድና የሴት አንድነት የፈጣሪ ልግስናና ፍሬያማነት በሥጋ መፈጸም ነው፡፡ “ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፤ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ፡፡”ዘፍ. 2፡24 የሰው ትውልዶች ሁሉ ምንጭም ይኸው አንድነት ነው፡፡

“ኢየሱስ የመጣው ፍጥረትን ወደ መጀመሪያ ንጽሕናው ለመመለስ ነው፡፡ በተራራው ስብከት ላይ “አታመንዝር” እንደተባለ ሰምታችኋል፡፡ እኔ ግን እላችኋለሁ፣ ወደ ሴት ያየ ሁሉ የተመኛትም ያን ጊዜ በልቡ ከእርስዋ ጋር አመንዝሯል” ማቴ. 5፡ 27-28 ሲል የእግዚብሔርን ሕግ በሚገባ ይተረጉመዋል፡፡ “እግዚአብሔር አንድ ያደረገውን ሰው ሊለያየው አይችልም፡፡” ማቴ.19፡6 ስድስተኛው ትእዛዝ የሰውን ፆታዊ ባህርይ በሙሉ እንደሚያካት በቤተ ክርስቲያን ትውፋት ዘንድ በሚገባ ግንዛቤ ተወስዶበታል፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት