እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የቤተ ክርስቲያን ማኅበራዊ ትምህርት

የቤተ ክርስቲያን ማኅበራዊ ትምህርት

ክርስቲያናዊው መገለጥ… የማኅበራዊ ኑሮን ሕግጋት ጠለቅ አድርጐ ለመረዳት ያግዛል፡፡” ቤተ ክርስቲያን ስለሰው እውነቱን ሁሉ ተገልጦ የምታገኘው ከወንጌል ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ወንጌልን የመስበክ ተልእኮዋን በምታከናውንበት ጊዜ በክርስቶስ ስም ስለ ሰብአዊ ክብር፣ ስለ ጥሪውና ስለሰዎች ሱታፌ ትመሰክራለች እንዲሁም ለመለኮታዊ ጥበብ በሚስማማ መንገድ ጽድቅን ሰላምን እንደሚሹ ሰዎችን ታስተምራለች፡፡

“መሠረታዊ ለሆነ ለግል መብቶች ወይም ለነፍሳት ደኅንነት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ” ቤተ ክርስቲያን ስለ ኤኮኖሚና ስለ ማኅበራዊ ጉዳይ ሥነ ምግባራዊ አስተያየትን ትሰጣለች፡፡ ሥነ ምግባራዊ ሥርዓትን በሚመለከት ቤተ ክርስቲያን ከፖለቲከኞች የተለየ ተልእኮ አላት፤ የጋራ ጥቅምን ለሚመለከቱት ምድራዊ ሁኔታዎችም ትኩረት ትሰጣለች፤ ምክንያቱም የመጨረሻ ግባችን ለሆነው ለገዢው በጐነት የተሰጡ ናቸውና፤ ምድራዊ ሃብቶችን በተመለከተ፣ ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶች አኳያ ትክክለኛ አመለካከቶችን ለመስገኘት ትጥራለች፡፡

የቤተ ክርስቲያን ማኅበራዊ አስተምህሮ የተስፋፋው ወንጌል ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ኅብረተሰብ የፍጆታ እቃዎችን ለማምረት የሚያስችሉት አዳዲስ አደረጃጀቶች፣ አዲሰ ኅብረተሰብን የሚመለከት ጽንሰ ሀሳብ፣ መንግሥትና ሥልጣን፣ እንዲሁም አዲሰ የሰራረኛና የባለቤትነት ደንቦች ያለው ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ኅብረተሰብ ይዞ ከፊቱ በተደቀነበት በአሥራ ዘጠነኛው ምእተ ዓመት ነው፡፡ የምጣኔ ሐብትና ማኅበራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ የትምህርት ቤተ ክርስቲያን መስፋፋት የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ዘለቄታ ያለው መሆኑን፤ አንዲሁም ሁልጊዜ ሕያውና እጅግ አስፈላጊ ለሆነው ለቤተ ክርስቲያን ትውፊትን ምስክርነቱን ይሰጣል፡፡

የቤተ ክርስቲያን ማህበሪዊ አስተምህሮ ቤተ ክርስቲያን በታሪክ ሂደት የሚከሰቱትን ሁኔታዎች በመንፈስ ቅዱስ ተራዳኢነት በኢየሱስ ክርስቶስ በተገለጸው ምላት አንጻር የምትተረጉምበት አንድ ራሱን የቻለ ትምህርት ቤተክርስቲያን ነው፡፡ ምዕመናኑ ይበልጥ በእርሱ ለመመራት ዝግጁ በሆኑ ቁጥር አስተምህሮ መልካም ፈቃድ ባላቸው ሰዎች ዘንድ በቀላሉ ተቀባይነትን ሊያገኝ ይችላል፡፡

የቤተ ክርስቲያን ማኅበራዊ ትምህርት የማሰላሰያ መርሖዎችን፣ የመመዘኛ ነጥቦችን ያቀርባል፣ የድርጊት መመሪያዎችን ይሰጣል፡፡

ማኅበራዊ ግንኙነቶችን ሙሉ በሙሉ በኤኮኖሚአዊ እንቅስቃሴዎች የሚወሰንበት ማንኛውም ሥርዓት ለሰብአዊ ፍጡርና ለሥራዎቹ ባህርይ ተቃራኒ ነው፡፡

ትርፍን እንደ ኢኮኖሚ ብቸኛ ጠባይና የእንቅስቃሴዎች የመጨረሻ ግብ አድርጐ የሚወስድ ንድፈ ሃሳብ ከሥነ ምግባር አኳያ ሲታይ ተቀባይነት የለውም፡፡ ለገንዘብ የሚኖር የተዛባ ፍላጐት መጥፎ ውጤቶችን ማስከተሉ አይቀርም፡፡ ማኅበራዊውን ሥርዓት ለሚያውኩ በርካታ ግጭቶች ምክንያት ከሚሆኑ አንዱ አፍቅሮተ ንዋይ ነው፡፡

የግለሰቦችን የቡድኖችን መሠረታዊ መብቶች ለሕብረት ሥራ የሚያስገዛ ሥርዓት ሰብአዊ ክብርን ይፃረራል፡፡ ሰውን እንደ ሰው ሳይሆን እንደ ትርፍ ማስገኛ መሣሪያ አድርጐ የሚቆጥር ማንኛውም ሥራ ሰውን ባሪያ ያደርጋል፡፡ ገንዘብን ወደማምለክ ያመራል፤ እግዚአብሔር የለም የሚለውን እምነት የማስፋፋት አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ “ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አይችሉም”

አምላክ የመካድ ርእዮተ ዓለማትን ቤተ ክርስቲያን አትቀበልም፡፡ እንደዚሁ ሁሉ “ካፒታሊዝም”ን ተግባራዊ በማድረግ ሂደት የሚንፀባረቀውን ግለኝነትንና የገበያ ሕግ በሠራተኛ ላይ ያለውን ፍፁም ቀደምትነትን አትቀበልም፡፡ ኤኮኖሚን በአንድ ማዕከላዊ አስተዳደር ሥር በሚያጠቃልል እቅድ ብቻ መቆጣጠር ማኅበራዊ ትስስርን ከመሠረቱ ያዛባል፡፡ ኤኮኖሚን በገበያ ሕግ ብቻ መቆጣጠር ማኅበራዊ ፍትሕን አያስገኝም፡፡ ምክንያቱም “በገበያ ሊሟሉ” የማይችሉ ብዙ ሰብአዊ ፍለጐቶች አሉና ነው፡፡ ከትክክለኛ የዋጋዎች ተዋረድና የጋራ ጥቅም አንፃር ገበያንና ኤኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን በአግባቡ መቆጣጠር የሚገደፍ ተግባር ነው፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት