እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ጾም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ

ጾም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ

በመጽሐፍ ቅዱሳዊ አገላለጽ ደግሞ ጾም ማለት ለእግዚአብሔር ክብር ሲባል ከምግብ ወይም ከውሃ በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ለተወሰነ ጊዜ በፈቃድ መከልከል (መታቀብ) 2ኛ ሳሙ.12፤17። እንዲሁም ነፍስን በእግዚአብሔር ፊት ዝቅ ማድረግ እንደሆነ  ያስቀምጣል።

ጾም በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት

በብሉይ ኪዳን ዘመን በተለያዩ ጊዜያትና ምክንያቶች የሰው ልጆች በጾምና በጸሎት እግዚአብሔር አምላክን ይማጸኑ ነበር (1ሳሙ.7፤6 1ነገ.21፤9)። “ደብዳቤውም እንዲህ የሚል ነበር፤ የአንድ ቀን ጾም አውጁ፤ ሕዝቡንም በአንድነት ሰብስቡ ለናቡቴም የክብር ቦታ ስጡት። በኀዘን ጊዜም እንዲሁ የሙሴ ሕግ የአንድ ቀን ብቻ ደንግጓል።  ሌዋ.16፤29-34 ከዚህ የሚከተሉትን መመሪያዎች በሚመጡት ዘመናት ሁሉ ቋሚ ሥርዓት አድርጋችሁ ትጠብቁታላችሁ። ሰባተኛው ወር በገባ በአስረኛው ቀን እስራኤላውያንና በእነርሱ መካከል የሚኖሩ መጻተኞች ራሳቸውን ማዋረድ አለባቸው፤ በዚያ ቀን ምንም ሥራ አይሥሩበት። በዚያን ዕለት ንጹሖች እንድትሆኑ የኃጢአት ማስተሰረያ ይደረግላችኋል። ከዚያ ከኃጢአታችሁ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት የነጻችሁ ትሆናላችሁ። ያም ዕለት እንደሰንበት የዕረፍት ቀን ይሁንላችሁ። በዚያም ቀን ራሳችሁን አዋርዱ ይህም የዘላለም ሥርዓት ነው። በአባቱ ምትክ ሊቀ ካህናት እንዲሆን ተለይቶ የሚሾመው ካህን የተቀደሰ የክህነት በፍታ ልብሱ ለብሶ ያስተሰርያል። እርሱም ለቅድስተ ቅዱሳኑ ለመገናኛው ድንኳን ለመሰዊያው ለካህናቱና ለጉባዔው ያስተሰርያል። በዓመት አንድ ጊዜ የእስራኤላውያንን ኃጢአት ሁሉ ማስተሰረያ የዘላለም ሥርዓት ይሆናል። ዘኁ.29፤7 ሰባተኛው ቀን በገባ በአስረኛው ቀን ለማምለክ ትሰበሰባላችሁ፤ በዚያን ቀን ምግብ አትመገቡም፤ ሥራም አትሠሩም።

ከባርነት ነጻ ከወጡ በኋላ አራት የጾም ቀናት ተጨመሩ (ዘካ.8፤19) የሠራዊት አምላክ እንዲህ አለኝ፦ በአራተኛው፣ በምስተኛው፣ በሰባተኛውና በአስረኛው ወር ትጠብቁት የነበረው ጾም ሁሉ ለይሁዳ ሕዝብ የተድላና የደስታ በዓል ይሆንላቸዋል፤ እናንተ ግን እውነትንና ሰላምን ውደዱ።

ጾም በአዲስ ኪዳን ውስጥ

desertoለአዲስ ኪዳን ዘመንም ለክርስቲያን ወገኖች የጾም አስፈላጊነት፣ ጥቅምና ሥርዓትን በተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ ተገልጸው እናገኛቸዋለን። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አገልጎት ከምጀመሩ አስቀድሞ በዮሐንስ እጅ ከተጠመቀ በኋላ ወደ በረሃ ሄደ፤ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ (ማቴ.4:)። በሌላ ስፍራ ደግሞ ኢየሱስ ራሱ ለደቀ መዛሙርቱ ስለጾም ሲያስተምር ጾም ለሰኦች ታይታ ተብሎ የሚፈጸም ሥርዓት ሳይሆን በስወር ከእግዚአብሔር አምላክ ጋር ብቻ የሚደረግ መንፈሳዊ ግንኙነት እንዲሆን በማስጠንቀቅ ጭምር ነው (ማቴ.6:16)።

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት