እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ጰራቅሊጦስ

ጰራቅሊጦስ

menfes_kidusሐዋርያት ኢየሱስ እንደሚተዋቸው ሲያውቁ አዘኑ፡፡ ኢየሱስ ግን “እሄዳለሁ ስላልኋችሁ ልባችሁ በሐዘን ተሞላ ነገር ግን እኔ ብሄድ ይሻላችኋል፡፡ ካልሄድኩ መንፈሰ ቅዱስ አይመጣላችሁም፡፡ ከሄድኩ ግን እልክላችኋለሁ” ዮሐ. 16፡6 “መንፈስ ቅዱስ ሲመጣ እውነትን ሁሉ ያስተምራችኋል” የሐዋ. 16፡13 “አባቴ ከእናንተ ጋር ለዘወትር የሚኖር አጽናኝ እንዲልክላችሁ እለምነዋለሁ” ዮሐ. 14፡15 “ከላይ የሚወርድ ኃይል መንፈስ ቅዱስ እስክትቀበሉ ድረስ በኢየሩሳሌም ቆዩ” ሉቃ. 24፡49 እያለ አበረታታቸው፡፡

እነርሱም ቃሉን አምነው ከእመቤታችን ማርያምና ከሌሎች ሴቶች ጋር በጽዮን አዳራሽ በጸሎት ተጠመዱ፡፡{jathumbnail off} በዚህም ሁኔታ ሲጠብቁት ሳለ ነፋስ የሚመስል ድምፅ ያሉበትን ቤት ሞላው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ ወረደ፡፡ በራሳቸውም ላይ የእሳት ነበልባል የሚመስሉ ነጸብራቆች ታዩአቸው፡፡ ሁሉም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ በተለያዩ ቋንቋዎችም መናገር ጀመሩ፡፡ የሐዋ 1፡12፤2፣1-14

“ከላይ ኃይል እስኪሰጣቸው ድረስ በኢየሩሳሌም ቆዩ” ብሎ ኢየሱስ ያዘዛቸው  ይህን ሰማያዊ ኃይል ካልተቀበሉ ሐዋርያት እውነተኛ ተከታዮች ስለማይሆኑ ነበር፡፡ መንፈስ ቅዱስ ባይወርድላቸው ኖሮ ኢየሱስ የሰጣቸውን ከባድ ኃላፊነት እክል ሲያጋጥማቸው በፈሩ፣ በርግገውም ኢየሱስን ትተውት በተበታተኑ ነበር፡፡ መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፡፡ በዚያን ጊዜ በኢየሩሳሌም፣ በይሁዳ ሀገር ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” እያለ ተንብዮላቸው ነበር፡፡ የሐዋ. 1፡8 ትንቢቱ በመንፈስ ቅዱስ መውረድ ተፈጸመ፡፡ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ሲወርድባቸው በመለወጣቸው መንፈሳዊ ሐሳብ አደረባቸው፤ ካለ ኢየሱስ በስተቀር ስለ ሌላ አይናገሩም፣ አያስቡም ነበር፡፡ በመጀመሪያ የነበራቸው ፍርሃት ጥርጣሬ ተወግዶ መንፈሳቸው ጽናትን አገኘ፣ እምነትና ብርታት ሞላባቸው፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ለብሰው ስለ ክርስቶስ በሁሉ ቦታ በግልጽ ሲሰብኩ፣ ለሰው ደኅንነትን ማብሰር ጀመሩ፡፡ ስብከታቸው ደግሞ ብዙ ፍሬ አፈራ፡፡ ነፍሳት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሳባቸው፡፡

እኛም ደግሞ በጥምቀት በሜሮን መንፈስ ቅዱስን ተቀብለናል፡፡ በእኛ ላይ ወርዶ ከኃጢአት ልጅነት የጽድቅ ልጆች አደረገን፡፡ ከእኛ ጋር አለ፣ ይመራናልም፡፡ በጸጋው አእምሮአችንን ያበራልናል ምኞታችንን ያሳካልናል፡፡ ሐዋርያት በጥሩ ዝግጅት ተቀብለውት እኛ ግን በቀዘቀዘ መንፈስ እንቀበለው ይሆን? በሐዋርያት ላይ ሲወርድ የቅድስና ፍሬ አሳየ፤ በእኛ ላይ ግን በበደላችን ምክንያት ያለ ቅድስና ፍሬ ይቀራል፤ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የግድ ያስፈልገናል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ሲመጣልን ተዘጋጅተን በልባችን እንቀበለው፡፡ በደንብ እናዳምጠው፡፡ በሙሉ ልባችን እንታዘዘው እናክብረው፡፡ በኃጢአታችን ከእኛ እንዳናርቀው እንጠንቀቅ፡፡

ምንጭ፡ መንፈሳዊ ማሳሰቢያ

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት