እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

“ከሚከፋፍለን ይልቅ አንድ የሚያደርገን የላቀ ነው!” ር.ሊ.ጳ ፍራንቼስኮስ (የክርስቲያኖች ኅብረት)

Patriarch Pope“ከሚከፋፍለን ይልቅ አንድ የሚያደርገን የላቀ ነው!” ር.ሊ.ጳ ፍራንቼስኮስ በቫቲካን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትሪያሪክ ዘኢትዮጵያን በተገናኙበት ወቅት በአጽኖዖት የተናገሩት ነው።
ብፁዕ ፓትሪያርኩ ካለፈው ዓርብ ጀምሮ በቫቲካን የተገኙ ሲሆን፡ በቫቲካን ውስጥ በ“ኮሌጆ ኢቶፒኮ” የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ተማሪ ካህናት በመኖሪያቸው አቀባበል እንዳደረጉላቸውና ተይዞ በነበረው መርኀ ግብር መሠረት በካቶሊካዊት ቤ/ያን የክርስቲያኖች ኅብረት እንቅስቃሴን ከሚያጠናክረው ምክር ቤት ጋር ስብሰባ ማካሄዳቸው ታውቋል። በቆይታቸውም በቫቲካን የሚገኘውን የሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ መቃብር እንደጎበኙና በኡርባኒያኑም ኮሌጅ ቤተ ጸሎት ፓትሪያርኩና በሮም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በጋራ ሥርዓተ አምልኮ ተካፍለዋል።
ር.ሊ.ጳ ፍራንቼስኮስ ሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት “ሁሉ ነገራቸው አንድ ነው ማለት ይቻላል” ምክንያቱም አንዲት እምነት፡ አንዲት ጥምቀትና አንድ አዳኝ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንጋራለንና በማለት ለፓትሪያርክ ማቲያስ ቀዳማዊ ንግግር አድርገዋል።
ር.ሊ.ጳ ፍራንቼስኮስ ሲቀጥሉም “እኛ በክርስቶስ ወንድማማቾችና እህታማቾች ነን፤ ብዙ ጊዜ እንደተስተዋለውም ከሚከፋፍለን ይልቅ አንድ የሚያደርገን የላቀ ነው” በማለት የሚሰማቸውን ቅርበት ገልጸዋል። በማያያዝም በተለያዩ መንገዶች የተለያዩ ክርስቲያኖችን በጋራ የሚቀበሏቸው ስቃዮች እንዴት ወደ በለጠ መቀራረብ እንዳመጧቸው በመናገር “በጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሰማዕታት ደም አዲስ ክርስቲያኖች ይግኙ ዘንድ ዘር በመሆን እንዳገለገለ ሁሉ ዛሬም የተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት አባላት ሰማዕትነት የክርስቲያኖች አንድነት ዘር ሆኗል” ብለዋል።
ር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ ይህንኑ የክርስቲያኖች መስዋዕትነት ለአንድነት አሁንም የሚያበረክተውን ጥቅም በማመልከት “የሰማዕታቱ አንድነት እኛ ወደ ላቀ የአንድነት ጎዳና እንድንጓዝ ይጠራናል” ሲሉ ሁለቱም አብያተ ክርስቲያናት ሰማዕታት እንዳሏቸው አስታውሰዋል።
በመቀጠልም ቤተ ክርስቲያን ሕዝባቸውን በሚያስተዳድሩ መንግሥታት ውስጥ ያላትን ሚና ሲገልጹ ር.ሊ.ጳ ፍራንቼስኮስ “የዓለምን ፖለቲካዊና ኤኮኖሚያዊ ሥልጣን የያዙትን ሰዎች አብሮ በሰላም ተቻችሎና ተከባብሮ በእርቅ በይቅርታና በመተባበር መኖርን ያስፋፉ ዘንድ መማጠናችንን አሁንም ቢሆን ማቋረጥ የለብንም” ሲሉ አሳስበዋል። አያይዘውም በዚህ ረገድ በኢትዮጵያ ያለው የተሻለ ማኅበረሰብ ለመፍጠር ሴቶችንም ያካተተውን ጥረት አመስግነው፡ “መንፈስ ቅዱስ ሆይ! ወደ ስምምነትና ሰላም በምናደርገው ጉዞ ላይ ብርሃንህን ስጠን ምራን!” የሚል ጸሎት በማሳረግ ደምድመዋል
ምንጭ- www.zenit.org

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት